በምትሰሩት ሥራ ሀፍረት አይሰማችሁ። ሰዎች ገበታችሁ ላይ ምግብ አያስቀምጡላችሁም ወይም የቤት ኪራይ፣ የልጆች ት/ት ክፍያ አይከፍሉላችሁም። ምንም ነገር አምናችሁበት እስከሰራችሁ ድረስ፣ ገቢ እስካገኛችሁበት ድረስ ለጊዜውም እንኳን ቢሆን ልትኮሩ ይገባችኋል። በሥራችሁ ትኮራላችሁ ማለት ግን ሁሌም በዚያ ሥራ ላይ ተመጣጣኝ ላልሆነ ክፍያ ትቆያላችሁ ማለት አይደለም። አንድ ቀን ጥረታችሁን የሚመጥን ሥራ፣ ዋጋችሁን የሚመዝን ሥራ ቦታ ያጋጥማችኋል።