በ2016 በጀት ዓመት ኩባንያችን ማህበራዊ ኃላፊነት ከመወጣት አንጻር የህብረተሰቡን ሁሉን አቀፍ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ሊያሻሽሉ የሚችሉ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል፡፡
በትምህርት፣ ጤና፣ የአካባቢ ጥበቃ፣ አረንጓዴ ልማት፣ ሰብአዊ ተግባራት እና የመንግስት ልማት ፕሮጀክቶች በዓይነት እንዲሁም በገንዘብ በድምሩ 694.2 ሚሊዮን ድጋፍ ተደርጓል፡፡
ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች 900ሺ የደብተር፣ በመላው ሀገሪቱ በሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላቋቋምናቸው 66 የዲጂታል መማሪያ ማዕከላት ነፃ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሁም በ42 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለሚገኙ 6000 ድጋፍ ለሚያሻቸው ተማሪዎች የኪስ ገንዘብ ተለግሷል፡፡
በተጨማሪም ባለፉት አምስት ዓመታት በ700 ጣቢያዎች 3.8 ሚሊዮን ችግኞች በመላ አገሪቱ በመትከል እና በመንከባከብ የጽድቀት መጠንን በአማካኝ 82% ለማድረስ ተችሏል፡፡ እንዲሁም በኩባንያችን ቤተሰቦች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች 7.6 ሚሊዮን ብር የገንዘብ እና የተለያዩ ቁሳቁስ ልገሳ ተደርጓል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡ https://bit.ly/3VWyKnZ
#SustainableDevelopment #CSR #Ethiotelecom #GSMA #ITU #WorldBank #OECD #G6countries #HOPR #HoF